All Posts By Superadmintest

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስተባባሪነት በክፍለ ከተማው የክረምት የበጎ ፈቃድ የሚታደሱ የአቅመ ደካማ ቤቶች የማስጀመሪያ መርሀ-ግብር ተካሄደ፡፡

H6

(ሀምሌ 30 ቀን 2016 ዓ.ም) በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አስተባባሪነት በክፍለ ከተማው ወረዳ 9 አስተዳደር በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚገነቡ 19 ቤቶችን የማስጀመሪያ መርሀ-ግብር ተካሂዷል፡፡  አዲስ አበባ ከተማ የህብረተሰብ ተሳትፎና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር አብርሃም ታደሰ በማስጀመሪያ መርሀ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በጎነት ወሰን የሌለው የአይምሮ ትልቅ እርካታ የሚያስገኝ እንደሆነ ጠቁመው በትምህርት ዘርፍ የተሰማሩ አካላት በበጎ...

ባለስልጣኑ ባደረገው ድንገተኛ ኢንስፔክሽን 44 ኮሌጆች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል፡፡

logo

 (ሀምሌ 25 ቀን 2016 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት በ2016 ዓ.ም ለ59 ኮሌጆች በተከናወነ ድንገተኛ ኢንስፔክሽን የተገኙ ግኝቶችን መሰረት በማድረግ 1.ከፍተኛ የስርዓተ ስልጠና ፖሊሲ ጥሰት እና የስትራቴጂ ጥሰት የታየባቸው 18 ኮሌጆች የታገዱ ሲሆን እነርሱም ብራይት ኮሌጅ ልደታ ካምፓስ ብራይት ኮሌጅ ጀሞ ካምፓስ ሸገር ኮሌጅ...

የባለስልጣኑ የውጭ ጥናት ግምገማ ተካሄደ፡፡

r3

  (ሀምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በውጭ አጥኚ ምሁራን ያስጠናውን "Factors affecting the achievements of grade 12 students in national exams in Addis Ababa" በሚል እርሰ-ጉዳይ የባለስልጥኑ አመራሮች፣የቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጆች እንዲሁም የባለስልጣኑ የትምህርት ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት ባለሙያዎች  በተገኙበት ግምገማ ተካሄደ፡፡  የባለስልጣኑ ምክትል ስራስኪያጅ አቶ አድማሱ...

ባለስልጣኑ የ2017 መሪ እቅድ ላይ እና የዝግጅት ምዕራፍ እቅድን የጋራ የማድረግና የማናበብ ተግባር አከናወነ፡፡

p8

    (ሀምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም) የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት መሪ አቅድ እና የዝግጅት ምዕራፍ እቅድን የጋራ የማድረግና የማናበብ ተግባር ተከናወነ፡፡  አቶ አድማሱ ደቻሳ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ የመድረኩን አላማ እንደገለጹት ለሁሉም የበጀት አመቱ ማስጀመሪያ እንደሆነ ገልጸው ፤በዋናው ቢሮ እና በቅ/ጽ/ቤት  በሁሉም ዘርፍ ያለው ባለሙያ እቅዱን  ተረድቶት በቂ መግባባት ላይ...

ለጊብሰን ዩዝ እና ማግኔት ቅ/አንደኛ፣አንደኛ፣መካከለኛ እና ሁለተኛ ት/ቤቶች ለጠየቁት ይቅርታ ምላሽ ተሰጠ፡፡

g1

ትምህርት ቤቶቹ የተማሪዎችን ምዝገባ ቀጥሎ የተቀመጡትን ነጥቦች አስተካክለው እንዲመዘግቡ ተፈቀደ፡፡ 1.ክብርት ከንቲባ ያስቀመጧቸውን የስራ መመሪያ እና አቅጣጫዎችን እንዲሁም የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የአሰራር አቅጣጫዎችን ህግና ስርአት በሚያዘው ብቻ ያለመሸራረፍ አሟልተው የመተግበር ግዴታ ያለባቸው መሆኑ፤2.የትምህርት ፖሊሲ፣ስርዓተ ትምህርት፣መመሪያዎችና አሰራሮችን ሙሉ ለሙሉ አሟልተውና አክብረው መተግበር እንዳለባቸው፤3.ለ2017 የትምህርት ዘመን እውቅና ፍቃድ እድሳት በሌላቸው(4) ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን መዝግበው እንዲቀጥሉ፤4.እውቅና...

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራን ለማስጀመር ከትምህርት ተቋማት ጋር የቤት እድሳት ርክክብ አደረገ፡፡

pic6 1

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራን ለማስጀመር ከትምህርት ተቋማት ጋር የቤት እድሳት ርክክብ አደረገ፡፡ (ሀምሌ 5 ቀን 2016 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራን ለማስጀመር በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከ ወረዳ 9 ለሚገኙ 19 የአቅመ ደካማ ወገኖች ቤት የማደስ ስራ ለማከናወን ርክክብ አድርጓል፡፡ በዚህም የክረምት በጎ...

ባለስልጣኑ "የምትተክል ሀገር የሚያጸና ትውልድ" በሚል መሪ ቃል 6ኛውን ዙር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተከናወነ።

c3

  ሀምሌ 13 ቀን 2016 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን "የምትተክል ሀገር የሚያጸና ትውልድ"በሚል መሪ ቃል 6ኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በዛሬው እለት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በለቡ ወረዳ የተካሄደ ሲሆን የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳኛው ገብሩ በመርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት...

ለመምህራንና ለትምህርት ቤት አመራሮች የሙያ ብቃት ምዘና በከተማ አቀፍ ደረጃ ግንቦት 1 ቀን የሚሰጥ መሆኑ ተገለጸ፡፡

news39

(ሚያዚያ 29 ቀን 2016 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮና የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በጋራ በመሆን የሚሰጠውን ከተማ አቀፍ የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች የሙያ ብቃት ምዘና አፈጻጸምን አስመልክቶ ውይይት አካሂደዋል፡፡ ምዘናው መንግስት ለትምህርት ጥራትና መሻሻል ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ በተሻለ ለመምራት የሚያስችል መሆኑን የገለጹት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ...

በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተከናወነ፡፡

1

ሚያዚያ 14 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2016 በጀት ዓመት አገልግሎት አሰጣጥ ያለበት ነባራዊ ሁኔታዎች በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል፡፡ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳኛው ገብሩ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደተናገሩት የውይይት መድረኩ አላማ ባለስልጣኑ በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር በማድረግ የሚታዩ ችግሮችን በአፋጣኝ ለመፍታት የሚያስችል...

በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና ተሠጠ፡፡

photo_2023-12-01_17-06-58

21/3/2016በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና ተሠጠ፡፡በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አዲሱ ስርዓተ ትምህርትን አስመልክት የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና ተሠጠ፡፡አቶ ዳኛው ገብሩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት ይህ ስልጠና መዘጋጀቱ ተቋማችን የትምህርት ጥራትን የማስጠበቅ ስራ ስለሚያከናውን ስርአተ- ትምህርቱ የለበትን ደረጃ በሚገባ ተገንዝቦና አውቆ ወደተግባር የሚተረጉም ባለሙያና አመራር በማስፈለጉ መሆኑን...